Posts

Showing posts from March, 2021

አንተ እግዜሩ አገረ-ኢትዮጵያ ሰው አጥታለችና አንተው ምራት!!

Image
  አንተ እግዜሩ አገረ-ኢትዮጵ ያ  ሰው አጥታለችና አንተው ምራት!! አንድ የአገራችን ምሁር በኦሮምያ እና አማራ ህዝቦች መካከል የነበረውን እና ስላለው የጠበቀ ዝምድና ሲያወራ አያይዞም ስለሚከሰቱ ግጭቶች ተናግሯል፡፡ “በአማራ እና ኦሮሞ ህዝቦች መካከል ያለው ከመጋባት ፣ ከማስረግ ፣ አብሮ ሃዘን ደስታን ከመካፈል ውጭ ምንም የልዩነት ታሪክ የለንም፡፡ እንደሚባለው እንኳ አለ ብለን ብናስብ የነበረው ፖለቲካዊ ስርዓት እንጅ ህዝቡን የሚመለከት አይደለም፡፡” ይሄነን ሃሳብ የፅሁፌ መነሻ ያደረግሁት አሁን በየአካባቢው የሚከሰቱ ዘርን ያነጣጠሩ ግድያዎችን … እያስተዋልን ባለበት ሰዓት መነሻቸው ምንድነው? ገዳይና ተገዳይ ስለምን እንደሚገዳደሉስ ያውቁታል ወይ? ሟች የሚሞትበትን ሰበብ ያውቀዋል ወይ? ገዳይ የሞት ሰይፍ የሚከነዳበትን ምክንያት ያውቀዋል ወይ? ከ1983 በፊትም ሆነ በኀላ የአገራችን ምሁራን በተለይም ስሙን ማስታወስ ያልቻልሁት አንድ ሰው ታሪካዊ ምክሮችን ለሞተው ጠቅላይ ሚኒስተር አካፍለው ነበር፡፡ የምሁሩ ማህበረሰብ የቻለውን ያክል ራሱን በማግለል ፣ በመተቸት ፣ በመቃወም የስርዓቱ አገር አፍራሽነት ተቃውሟል፡፡ መክሯል ዘክሯል፡፡ የዘር ፖለቲካ ዞሮ ዞሮ የዘር ፖለቲካ ነው፡፡ በአንድ ወቅት የንጉሱ ስርዓት ጎጃምን ጨፍጭፎ ነበር፡፡ ” ሞጣ ቀራኒዮስ ምነው አይታረስ በሬ ሳላይ መጣሁ ከዚያ እስከዚህ ድረስ ” ተብሎም ተዘምሯል፡፡ ነገር ግን ቂምም ይሁን የተተከለ ቁርሾ ቅሬታ ጎጃም ውስጥ የለም፡፡ ቢኖር እንኳ የአገሪቱን ንጉሳዊ አስተዳደር ማውገዝ እንጅ የሰራዊቱን ዘር ፣ ማንነት ያጥላላ ወይም ለይቶ የተቃወመ አልነበረም፡፡ የሰዓቱን ፖለቲካ በበላይነት የሚጋልብ የበላይ ዘር ስላልነበረ ንጉሱ ተቆጡ ከማለት ውጭ የተለየ ሆኖ ወደ ማህበረሰቡ ጠልቆ ገብ...

ኦሮማራ

Image
ኦሮሞና አማራ ከኦህዴድና ብአዴን በጋራ ድምረት በሚል የግል አስተያትና ትዝብት ፣ መላምትና ስጋትን ለማካፈል ፅሁፉ ትኩረት ያደርጋል፡፡ የኦሮማራ ፈተናዎችና መፍትሄዎች ምን አንደሆኑ ለመቃኘት ይሞክራል፡፡ ብአዴን ከኦህዴድ በምን ፍጥነት እየተራመደ እንደሆነም ይነካካል፡፡ የኦህዴድ ሞተር ሆኖ የተገጠመለት የኦሮሞ ህዝብ ከሆነ የብአዴን ህዝባዊነትን በተግባር መዋሃድ ላይ ምን ውስንነቶችና ችግሮች ለማየት ይሞከራል፡፡ በመላምትነት የመደመር የዶ/ር አብይ ፖለቲካ ኦሮ-ማራ ሲደመር ኦህ-አህዴን ስሌት ምን ያህል ነው? ኦሮማራ የተከበረ እና የነበረውን የህዝብ ለህዝብ ትስስሩን አጠናክሮ የጣልቃገብ ጥላቻ ፖለቲካውን ድንበር ጥሶ መሻገር ችሏል፡፡ በርካታ ማሳያዎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ የደሴና ነቀምት የእግርኳስ ጨዋታ የባለሜዳዎች አቀባበልና መስተንግዶ ፣ የጣናኬኛ ዘማቾችና የጎጃሜዎች የደብረማርቆሱ ፣ የፍኖተሰላም ፣ የኢንጅባራው አቀባበል ፣ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የጋራ የተቃውሞ ተመሳሳይ ድምፆች ፣ የፋሲል ከነማና አዳማ ከነማ ጨዋታ የናዝሬቶቹ አቀባበል በፍቅር የተለወሰ ፣ የዘላለም አብሮ መኖር ስንቅ የሆነ ነው፡፡ ጎንደር ላይ የኦሮሞው ህመም የሚጠዘጥዘው አማራ ፣ አዳማ ላይ የአማራው መጨፍጨፍ የሚያመው ኦሮሞ ለዚህም ድምፁን ከፍ አድርጎ የሚያሰማ ኦሮማራ ተገንብቷል፡፡ ይሄ ጭንቅና ችግር ድንገት ዛሬ የወለደው ሳይሆን ከአፄዎቹ ጀምሮ ከሃረርጌ፣ ከሸዋና ወለጋ ጎጃም ድረስ ፣ በወሎ ከሚሴና ከረዩን አጠቃሎ በደምና በስጋ የተሳሰረ ፣ የአድዋ የነፃነት መስዋዕትነት ከፍሎ ያገኘውን ድል በጋራ ያጣጣመ ትውልድ ስለሆነ ነው፡፡ የአሁኑ እንደ አዲስ የመገለጡ ነገር የጥላቻ ሃውልትን በመካከላቸው እየገነባ ሲያበላላ የነበረው ” ጠባብና ትምክህተኛ” የሚል ለምድ ደርቦ የአናሳ አስተሳሰብ ፖለ...

በርሃብና ኀላቀርነት የምንገረፍበት አለንጋ አንሶን በራሳችን ላይ የዘረኝነት ጅራፍ የምንጨምር ምን ያልታደልን ብንሆን ነው ?

በርሃብና ኀላቀርነት የምንገረፍበት አለንጋ አንሶን በራሳችን ላይ የዘረኝነት ጅራፍ የምንጨምር ምን ያልታደልን ብንሆን ነው ? …አንዳንዴ  ” አህያ አባትህ ማነው ሲባል ፈረስ አጎቴ ነው”  አይነት መልስም ያዋጣልና፤ አገርህን  ስትጠየቅ ስለቀኝ ግዛት ታነሳና በአድዋ ድል በኩል አድርገህ በአፍሪካ አባት ጃንሆይ በኩል (ራስታ/ራስ ተፈሪ / ጋሽ ቦብ ማርሌይ/ ጃማይካ ብለህ ትቀበጣጥርና በአረንጓዴ ቢጫ ቀዩ የሬጌ ቆብ በኩል ዘልቀህ እሱ የፓን አፍሪካ የጥቁር ህዝብ የነጻነት ቀለም ነው ብለህ ለመሹለክ ሞክር፡፡ ያን ጊዜ ምዕት አመታት የእሱን አገር መገዛት እያሰበ ባንተ ነፃነት ሲደመም “ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ” ከርሃብ መርዷዊ ዜናህ ታመልጣለህ፡ ፡ (አልስቅም) =========================================== . ..ይህንንም አስጠላችሁን ፣ አስገደላችሁን ፣ እኛን አትወክሉም ፣ ስማችንን አትጥሩን በሚል አቋም በገሃድ በማንጸባረቅ ህዝባዊነትን መቀላቀል ይቻላል፡፡ ስርዓቱ በወለደው ጉድ ህዝብ ራቁቱን ወጥቶ ሃዘኑን እየገለፀ ፤ ጥቁር ለብሶ አደባባይ በአርምሞ ድምፁን እያሰማ ፣ በየቀኑ ለምን ሰው ተገደለ ሳይሆን ስንት እንደሞተ የሟች ብዛት እየሰማን በምንዉልበት አገር ላይ ምንም እንዳለልተፈጠረ ፀጥ ረጭ ማለት ዠጎረቤት ጎጆ ሲቃጠል እያዩ እንደማላገጥ ይቆጠራል፡፡ ሁላችንም ኢትዮጵያዊያን ነን፡ እንተሳሰብ፡፡ የአንዳችን መጉደል ለሁላችንም ጉድለት ነው፡፡   ከመለስተኛዋ ሱናሜ ምድር አንቀጥቅጥ ሳምንት በሰላም በመመለስና ልብ በማጋባት ዝም ወደማያስብለው የአገሬ ጉዳይ ተመልሻለሁ፡፡ በዚህ ፅሁፌ ውስጥ ግራ መጋባቴን ፣ ውርደት/ ሽንፈቴን ፣ ትዝብትና የአብሮ...

ከአንጀት ከሆነ እንባ አይገድም

Image
  ግርማው አሸብር (የማዕበሉ ውጤት) /  EDIT ነጻ ሃገር ነኝ በላቸው፡፡ ቋንቋ፣ ባህል፣ ፊደልና ጀግና ህዝብ አለኝ በላቸው፡፡ ያለ ጅሃድ ጦርነት እስልምናን ተቀብላ ባህልና ወጓ ያደረገች የቀደምት የክርስትና ምድር ናት ሃገሬ ስትላቸው ማንነትህ ይገባቸዋል፡፡ ስለ ቡናህና የሰው ልጅ መገኛነቷ ስትነግራቸው፣ ስለታላቁ የአፍሪካ አባት ግርማዊ ራስ ተፈሪ ስትነግራቸው ያኔ አንተ ትገለጥላቸዋለህ፡፡ በግርማው አሸብር ኢትዮጵያዊነት ሸጋ ነው ፡፡  ያኮራል፤ ከሰው በላይ ነው ልዕልናው፡፡  በዚሁ ሩቅ ምስራቅ ኢንዶኔዝያ ሃገር በተዘጋጀ  ግሎባል የባህል ፉስቲቫል ላይ አንድ ኢትዮጵያዊ ተገኝቻለሁ፡፡ ሊኖሩ የሚችሉትን አጋጣሚዎች ሁሉ ተጠቅሜ ኢትዮጵያን ስወክል ትልቅ ማንነት ተስተጋብቶብኛል ፤ እናንተም ብትሆኑ ኢትዮጵያዊነት ይዋረሳችኋል፡፡ ያው የውርስ ሃገር አይደል ያለን፡፡ ከእነዚያ ታላላቆች የወረስናት፡፡ ከቀማኛዎች እጅ ሳትገባ ህይወት ከፍለው ያወረሱን፡፡ Ethiopia defeated the Italian colonial army in the battle of Adwa. የሚል ጽሁፍ ሳነብ ኢትዮጵያ ቀኝ ሊገዟት የመጡትን ጣሊያኖች ደፍታ መለሠቻቸው ብየ ነው ምረዳው፡፡/ defeated = ደፏቸው ሃሃሃ… በዝግጅቱ ላይ ከ30 በላይ የዓለም አገራት ኢትዮጵያን ጨምሮ ተሳትፈዋል፡፡ ኢንዶኔዥያ፣ ኢትዮጵያ፣ ህንድ፣ ፓኪስታን ፣ አሜሪካ ፣  ጀርመን፣ ቻይና፣ ባንድላዲሽ፣ ሰሜን ኮሪያ፣ ጃፓን፣ ካምቦጅያ፣ ታይላንድ፣ ቱርኪሚኒስታን ፣ ማሊ፣ ታንዛኒያ፣ ስሎቫኪያ፣ታንዛኒያ፣ ኡጋንዳ፣ ማዳጋስካር፣ ሆላንድ፣ግብጽ፣ሱዳን፣ፖላንድ፣ አውስትራሊያ፣ሲንጋፖር፣ ማሌዥያ፣ ራሺያ፣ ቱርኪሚኒስታን እና ለቴሎችም አለኝ ያሉትን መገለጫዎቻቸውን ይዘው ቀረቡ ተሳትፈዋል፡፡ ...

“ትልቅ ስለነበርን ትልቅ እንሆናለን?”

  “ትልቅ ስለነበርን ትልቅ እንሆናለን?” JANUARY 14, 2018  /  ግርማው አሸብር (የማዕበሉ ውጤት)   /  EDIT በትውልድ ስማቸው ካሳ ኃይሉ፣ በፈረስ ስማቸው አባ ታጠቅ፣ በወታደራዊ ስማቸው መይሳው ካሳ እና እንዲሁም አንድ ለእናቱ ተብለው የሚታወቁት የ18ኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ ወታደርና ፖለቲከኛ አጤ ቴዎድሮስ ጥር 6 ቀን 1811 ዓ.ም. ሻርጌ በተባለ ቦታ ቋራ ውስጥ፣ ከጎንደር ከተማ በስተ ምዕራብ ከዛሬ 199 ዓመት በፊት ተወለዱ። ከበደ ሚካኤል ጃፓን እንደምን ሰለጠነች በሚለው መጽሃፋቸው ” የዛሬዋ ጃፓን ከዳግማዊ ቴዎድሮሷ ኢትዮጵያ ጋር እኩል በ1855 የኢንዱስተሪውን አቢዮት ተቀላቀሉት፡፡” ሲል ጽፏል፡፡አሁን ጃፓን የሮኬት ማ/ፋሽኖችን እያማረጠች የምዕራቡን አለም በአይኗ ቂጥ የምትመለከት ፣ የአለምን የቴክኖሎጂ ገበያ ቀጥ አድርጋ የተቆጣጠረች ሆናለች፡፡ ታዲያ ኢትዮጵያም የቴዎድሮስን ራዕይ በእልፍኙ ያሳደገው ዳግማዊ ሚኒልክ ተቀብሎ ሃገሪቱን አዘምኗታል፡፡ ፦ የዞረብንን አስማት ባናውቀውም አሁን ከያዘን ቁራኛ ስርዓት ጋር ተዳምሮ “ትልቅ ነበርን ትልቅ እንሆናለን”ን አማረብን ብለን እንዘምራለን፡፡ ሌሎች አገሮች የነበሩበትን ታሪክ አይደለም ዳግም ሊኖሩት ሊያስቡት ትግስት የላቸውም፡፡ ለምሳሌ ኢንዶኔዥያ 350 አመታትን በኔዘርላንድ ቅኝ ግዛት ውስጥ ቆይታለች፡፡ በኀላም ጃፓን አፈር ደሜ አስግጣ ገዝታታለች፡፡  713 አገር በቀል ቋንቋዎችና በወረራም ይሁን በስልጣኔ ሰበብ ወደአገራቸው የገቡ 6 መጤ ቋንቋዎች አሏት፡፡ ይሁን እንጂ ከነፃነቷ በኀላ ለህዝቦቿ አንድነት ይበጅ ዘንድ የራሷን ብሔራዊ ቋንቋ ከአገር ውስጥ ቋንቋዎች አዳቅላ ፈጥራ በ1945 በማወጅ ከመጀመሪያው ደረጃ ትምህርት አስከ ፍልስፍና ደረ...