አማርኛ ቋንቋና ኢትዮጵያ
አማርኛ ቋንቋና ኢትዮጵያ FEBRUARY 9, 2018 / ግርማው አሸብር (የማዕበሉ ውጤት) / EDIT በየትኛውም ቋንቋ የትኛውንም የግል ሃሳብና አመለካከት ማንፀባረቅ ፤ ለምንም አላማ መጠቀም መቻል የአማርኛ ቋንቋ ባህሪ ብቻ ሳይሆን የቋንቋ ተፈጥሮ ነው፡፡ ከአራት አመታት በፊት ደቡብ ክልል አማርኛ እንደሁለተኛ ቋንቋ ሳስተምር ቋንቋውን መናገርና መግባባት የሚችሉት ተማሪዎች ያላቸው በራስ የመተማመን ስሜትና ደስታ በጣም ትልቅ ነው፡፡ ባደረግሁት የዳሰሳ ጥናትም ምክንያቱ የአገሪቱን የስልጣኔ ቋንቋ መናገር በመቻላቸው እና ከከተማ የመጣ ሰው ጋር መግባባት በመቻላቸው እንደሆነ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ፡፡ ያው እንግሊዘኛ የሚፈጥረው አይነት ስሜት፡፡ ነገር ግን ከወደ ትልልቅና በእድሜ ከፍ ያሉ በተለይም ከወረዳ አመራርና ምናምን ጀምሮ ፣ አንዳንድ አካባቢም ዩኒቨርሲቲዎች አካባቢ ቋንቋውን የማጥላላት ነገር አለ፡፡ ይሔ በጥቅሉ የተሳሳተ ግንዛቤና የወቅቱ የሽቀላ ፖለቲካ የሰራው መርዝ ነው፡፡ በዚህ የማህበረሰብ ክፍል ላይ ጥናት ባይደረግም የነፍጠኛ ቋንቋ እየተባለ በደፈናው ጭፍን ጥላቻ ተነዝቶበታል፡፡ ህፃናት በአፍ መፍቻቸው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን እንዲማሩ የካናዳ ፣ አሜሪካ ፣ አውስትራሊያ እና ሌሎቹም አገራት በ1960ዎቹ አካባቢዎችና ቀደም ብሎም ጀምረው ለጊዜው መንገራገጮች ገጥሞት የነበረ ቢሆንም በምርምሮችና ማስታረቂያ ፖሊሲዎች በመቅረጽ ስኬታማ መሆናቸውን የቋንቋና ማህበረሰብ ተመራማሪዎች (sociolingust) የጥናት ውጤት ያሳያል፡፡ እንደኛ አገር ህፃናትን በአፍ መፍቻቸው አካባቢያቸውን እንዲያውቁ/ጠንካራ ግንዛቤ እንደኖራቸው በሚል ጠቃሚ መሰረት የተጀመረው የትምህርት ፖሊሲ አተገባበሩ ዘረኝነትን መሰረት አድርጎ በ...